Перейти к содержимому

Exit Exam and Remedial Exam

Muja Mercury

0:00 / 0:00

Exit Exam and Remedial Exam

4 436 просмотров · 3 года назад
Muja Mercury
59,4 тыс. подписчиков
4 436 просмотров · 3 года назад
የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማህበር ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶ/ር አረጋ ይርዳው ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ ካነሷቸው ነጥቦች... የመውጫ ፈተና የሚፈተኑት ተማሪዎች ከዓመታት በፊት የከፍተኛ ትምህርታቸውን ሲጀምሩ የመውጫ ፈተና የሚባል ነገር አልነበረም።ዘንድሮ በድንገት የመውጫ ፈተና ይሰጣል ተብሎ በመምጣቱ በተማሪዎች፣በተቋማት እንዲሁም በራሱ በትምህርት ሚኒስቴር ላይ ከፍተኛ ጫና ማሳደሩን ገልፀው ድንገተኛ ፈተና በመፈተን የትምህርት ጥራት ይመጣል የሚለው ነገር ብቻውን መፍትሔ ነው ብለው እንደማያስቡ ገልፀዋል። በተለያየ መልኩ ኮታ ይሙላ በሚል በገፍ ሲያልፉ የነበሩ ተማሪዎችን ድንገተኛ ፈተና በመስጠት የትምህርት ጥራት አይመጣም ያሉት ፕሬዚዳንቱ በአንፃሩ እሳቸው የትምህርት ሚኒስቴርን ቢመሩ ኖሮ #Exit_Exam መኖሩን ይፋ የሚያደርጉት ዘንድሮ ፍሬሽማን ለሚጀምሩ ተማሪዎች ሲሆን ፈተናውም ከአራት ዓመት በኋላ እንዲሰጥ ያደርጉ እንደነበር ገልጸዋል። ከቀናት በኋላ የሚሰጠውን የመውጫ ፈተና አስመልክቶ ልክ እንዳለፈው የ12ኛ ክፍል ፈተና የውጤት ማሽቆልቆል ይከሰታል ብለው ያስባሉ? በሚል ለቀረበላቸው ጥያቄ እንዲህ ብለዋል "አዎን (ብዙ ተማሪዎች ይወድቃሉ የሚል ስጋት አለኝ)።እነዚህ ተማሪዎች የተጨለፉበት መንገድ Suddenly Exam ስለመጣ ተዓምር ተፈጥሮ አዲስ እውቀት አላቸው ማለት አይደለም። ስርዓቱ በጠቅላላ እንጂ መፈተሽ ያለበት አንድ ቦታ ላይ ብቻ አይደለም።" ብለዋል። Remedial ተማሪዎችን በተመለከተ የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማህበር ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶ/ር አረጋ ይርዳው ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር በነበራቸው ቆይታ ካነሷቸው ነጥቦች ፨የሪሜዲያል ማጠቃለያ ፈተና 30% በተቋማት የሚሰጥ ሲሆን ፥ 70% የሚሰጠው በትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቶ ወደ ተቋማት እንደሚላክና ተቋማት በራሳቸው ሙሉ ሃላፍትና ተስጥቷቸው በመፈተን ለትምህርት ሚንስቴር እንደሚልኩና እርማቱንና ሌሎች ጉዳዮችን ትምህርት ሚንስቴር ይፋ እንደሚያደርግ መገለፁን ጠቅሰዋል። ፨የሪሜዲያል ውጤታቸው 50% እና ከዚያ በላይ የሚያመጡ ተማሪዎች ወደ ሚፈልጉት የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በመሄድ ቀጣይ ዓመት ፍሬሽማን መሆን የሚችሉ ሲሆን መንግስት ግን (የመንግስት ዩንቨርስቲዎች) የመቀበል ችግር ሊኖርበት ስለሚችል ከግል ወደ መንግስት ዩንቨርሲቲዎች የመግባት እድሉ ጠባብ መሆኑን ከትምህርት ሚኒስቴር እንደተነገራቸው ፍንጭ ሰጥተዋል