DW Amharic የነሐሴ 23 ቀን 2018 የዓለም ዜና
DW Amharic
0:00 / 0:00
DW Amharic የነሐሴ 23 ቀን 2018 የዓለም ዜና
1 820 просмотров · 1 час назад
DW Amharic
179 тыс. подписчиков
1 820 просмотров · 1 час назад
የነሐሴ 23 ቀን 2018 የዓለም ዜና
• በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር ፍራንክ ጋርሺያ ወደ ኢትዮጵያ ሊያቀኑ ነው። ጋርሺያ ባለፈው ግንቦት ወር ከተሾሙ ወዲህ ኢትዮጵን ሲጎበኙ የአሁኑ የመጀመሪያቸው ይሆናል።
• የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ-መንበር ማሕሙድ አሊ ይሱፍ በደቡብ ሱዳን ኢትዮጵያውያን ሰላም አስከባሪ ወታደሮች የተገደሉበትን ጥቃት አወገዙ። የደቡብ ሱዳን ባለሥልጣናት በጆንጊሌ ግዛት ከአራት ቀናት በፊት የተፈጸመውን ጥቃት በአፋጣኝ እንዲመረምሩ፤ ፈጻሚዎቹንም ለሕግ እንዲያቀርቡ ማሕሙድ አሊ ይሱፍ ትላንት አርብ ባወጡት መግለጫ ጥሪ አቅርበዋል።
• የአርባ ምንጭ ከተማ ፖሊስ “በሕገ-ወጥ መንገድ ሲዘዋወሩ የነበሩ” ያላቸውን 32 ኤርትራውያን በቁጥጥር ሥር እንዳዋለ አስታወቀ። በቁጥጥር ሥር ከዋሉት መካከል ሰባት ሕጻናት ይገኙበታል።
• በኒጀር አማጺ ወታደሮች በቁልፍ ወታደራዊ የጦር ሠፈርና የፕሬዝደንቱ መኖሪያ በሚገኝበት አካባቢ ላይ ተኩስ ከፈቱ።
• ሩሲያ ከኪየቭ አቅራቢያ በሚገኝ መጋዘን ላይ በድሮን በፈጸመችው ጥቃት 37 ሰዎች መገደላቸውን የዩክሬን ባለሥልጣናት ገለጹ። በጥቃቱ ከ40 በላይ ሰዎች መቁሰላቸው ተዘግቧል።
• ኔፓልና ቲቤት በሚዋሰኑበት ተራራማ አካባቢ በደረሰው የደራሽ ጎርፍ አደጋ መሞታቸው የተረጋገጠ ሰዎች ቁጥር 682 ደረሰ። በአደጋው አሁንም ወደ 3,000 የሚደርሱ ሰዎች የገቡበት የማይታወቅ በመሆኑ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር ይችላል ተብሎ ይጠበቃል።