የግብፅ ክስና የኢትዮጵያ መልስ… የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል… ግብፅን የፀጥታው ምክር ቤት አይሰማትም! #የሀገርጉዳይ
EBC
0:00 / 0:00
የግብፅ ክስና የኢትዮጵያ መልስ… የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃል… ግብፅን የፀጥታው ምክር ቤት አይሰማትም! #የሀገርጉዳይ
4 006 просмотров · Трансляция закончилась 1 день назад
EBC
2,16 млн подписчиков
4 006 просмотров · Трансляция закончилась 1 день назад
የሕዳሴ ግድብ በተመረቀ 1ኛ ዓመቱ ዋዜማ ላይ ቆመንም እኔ ብቻ ልጠቀም ባይዋ ግብፅ ጉዳዩን ወደ ፀጥታው ምክር ቤት ካልወሰድኩት ስትል ትሰማለች፡፡ በሀሰተኛ መረጃ ላይ የሚመሰረተውን ክሱን በተደጋጋሚ ወደ ምክር ቤቱ ወስዶ ያሰበውን ያላገኘው የካይሮ መንግሥት ከዓለም ዐቀፍ ሕግ በተቃራኒ መርህ ቆሞ ኢትዮጵያን ያዳክሙልኛል ያላቸውን የውስጥና የውጭ ኃይሎች እየደገፈ በዓባይ ወንዝ ጉዳይ የምክንያታዊና ፍትሓዊ ተጠቃሚነት ዓለም አቀፍ መርህ ላይ የቆመችውን ኢትዮጵያ በየቀኑ ይከሳል፡፡ ኢትዮጵያን በፈጠራ መረጃ ጋጋታ እየከሰሰች እና ከበባ ውስጥ ለማስገባት የምትችለውን ሁሉ እያደረገች ያልተሳካላት ግብፅ ማመን ያልቻለችውና ልታምን የሚገባው ሃቅ የሕዳሴ ግድብ ተገንብቶ መጠናቀቁን፤ ንግግር ያስፈልጋል ከተባለም ንግግሩ በአፍሪካ ኅብረት በኩል ብቻ መሆኑን ነው ይላሉ የግብፅን የጥፋት ሴራ አደባባይ ላይ ያሰጡት ለህንዱ ፈርስት ፖስት እንግዳ ሆነው የቀረቡት ዶክተር ማሲንጋ ሄልስንኪ፡፡ የሀገር ጉዳይ በዛሬ ዝግጅቱ የግብፅን የሴራ መንገድ በተጨባጭ ማስረጃዎች እየሞገተ የኢትዮጵያን አሸናፊነትና በትብብር የማደግ መርህ ይመለከታል፡፡