DW Amharic የጳጉሜ 02 ቀን 2018 የዓለም ዜና
DW Amharic
0:00 / 0:00
DW Amharic የጳጉሜ 02 ቀን 2018 የዓለም ዜና
3 030 просмотров · 2 часа назад
DW Amharic
180 тыс. подписчиков
3 030 просмотров · 2 часа назад
• የትግራይ ክልል ከፌድራል መንግሥት ጋር ሁለተኛ ጦርነት እንዳይቀሰቀስ ሽምግልና የጀመሩት የአፍሪካ ኅብረት ልዩ ልዑክ ኦሊሴጉን ኦባሳንጆ “ገለልተኛ አይደሉም” በማለት ወነጀለ።
• በኢትዮጵያ ውጊያ የገጠሙ ኃይሎች በሲቪል ሰዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን እንዲያቆሙ እና ዓለም አቀፍ ሕግ እንዲያከብሩ የተባበሩት መንግሥታት የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽነር ፎልከር ቱርክ ጥሪ አቀረቡ።
• የዩናይትድ ስቴትስ የልማት ፋይናንስ ኮርፖሬሽን (DFC) በቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያና በዙሪያው ከሚደረጉ ግንባታዎች ጋር ለተያያዙ አነስተኛና መካከለኛ ኢንተርፕራይዞች የሚሰጠውን ብድር ለማበረታታት ከፍተኛ መጠን ያለው ኢንቨስትመንት ለመመደብ ዕቅድ እንዳለው የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት አስታወቀ።
• የጀርመን መራኄ መንግሥት ፍሬድሪሽ ሜርስ ቀኝ አክራሪው አማራጭ ለጀርመን በዛክሰን አንኻልት ግዛት ያስመዘገው የምርጫ ድል ፓርቲያቸውን ከሥር ከመሠረቱ እንደነቀነቀ ተናገሩ። ቀኝ አክራሪው ፓርቲ በበኩሉ ግዛቲቱን የሚያስተዳድር ጥምር መንግሥት ለመመሥረት ከሌሎች ፓርቲዎችና የምክር ቤት አባላት ጋር ድርድር እንደሚያደርግ አስታውቋል።