Tamirat Haile 8 ታምራት ፡ ኃይሌ : ኢየሱስ ፡ ነካኝ ፡ በድንገት (Eyesus Nekagn Bedenget) (Vol. 8)
Ethiopian Protestant mezmur
0:00 / 0:00
Tamirat Haile 8 ታምራት ፡ ኃይሌ : ኢየሱስ ፡ ነካኝ ፡ በድንገት (Eyesus Nekagn Bedenget) (Vol. 8)
179 305 просмотров · 5 лет назад
Ethiopian Protestant mezmur
13 тыс. подписчиков
179 305 просмотров · 5 лет назад
በአዝመራ ፡ ጊዜ ፡ መኝታ (Beazmera Gizie Megneta)
እለምንሃለሁ ፡ አንድ ፡ ነገር (Elemenehalehu And Neger)
በቀኑ ፡ መጨረሻ (Beqenu Mecheresha)
ማንን ፡ እንደጣለ ፡ ይጥልሃል (Manen Endetale Yetelehal)
አንድ ፡ ነገር ፡ አውቃለሁ (And Neger Awqalehu)
ጌታ ፡ ሆይ ፡ አንድ ፡ ሰው ፡ ስጠን (Gieta Hoy And Sew Seten)
በሞቱ ፡ እንድመስለው (Bemotu Endemeslew)
አምንሃለሁ (Amnehalehu)
ጌታቸው ፡ በመጣ ፡ ጊዜ (Gietachew Bemeta Gizie)
ዲያቢሎስ ፡ ምነው ፡ ቸኮለ (Diyabilos Menew Chekole)
አዝ፦ በአዝመራ ፡ ጊዜ ፡ መኝታ ፡ በጽሞና ፡ ጊዜ ፡ ጫጫታ
የሰልፍ ፡ ነው ፡ የድል ፡ ይህ ፡ ሁሉ ፡ እልልታ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ማስተዋልን ፡ ስጠን ፡ ጊዜ ፡ እንዳያመልጠን
መከራው ፡ እግሩን ፡ ከማውጣቱ ፡ አቆምን ፡ መንበርከክ ፡ በፊቱ
የጸሎት ፡ መሰዊያ ፡ አፈረስን ፡ መስሎናል ፡ ሰማይ ፡ የደረስን
የምድረበዳው ፡ ትውልድ ፡ በውነ ፡ በወጉ ፡ አያውቅም ፡ ፡ ጦርነት
መሬትን ፡ አልረገጠም ፡ በእግሩ ፡ አታሎት ፡ እሩጫው ፡ ግርግሩ
አዝ፦ በአዝመራ ፡ ጊዜ ፡ መኝታ ፡ በጽሞና ፡ ጊዜ ፡ ጫጫታ
የሰልፍ ፡ ነው ፡ የድል ፡ ይህ ፡ ሁሉ ፡ እልልታ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ማስተዋልን ፡ ስጠን ፡ ጊዜ ፡ እንዳያመልጠን
እርስ ፡ በርስ ፡ እየተሟሟቅን ፡ ነፍሳትን ፡ ተዘርፈን ፡ አለቅን
መርከቡ ፡ መልህቁን ፡ ዘርግቶ ፡ ይጣራል ፡ ተሳፋሪ ፡ ጠፍቶ
ይቺ ፡ አለም ፡ ካልደረስንላት ፡ ጨውና ፡ ብርሀን ፡ የላት
ህመሟ ፡ ሄደ ፡ እየቀጠለ ፡ መድሀኒት ፡ በእጃችን ፡ አለ
አዝ፦ በአዝመራ ፡ ጊዜ ፡ መኝታ ፡ በጽሞና ፡ ጊዜ ፡ ጫጫታ
የሰልፍ ፡ ነው ፡ የድል ፡ ይህ ፡ ሁሉ ፡ እልልታ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ማስተዋልን ፡ ስጠን ፡ ጊዜ ፡ እንዳያመልጠን
ተባባልን ፡ እኔ ፡ ካንተ ፡ አላንስም ፡ ታወቅን ፡ ጌታ ፡ ባልሰጠን ፡ ሥም
ተራራቅን ፡ አጥር ፡ እያጠበቅን ፡ ለፍቅር ፡ ክፍያ ፡ ጠየቅን
በእልህ ፡ ሳይሰፋ ፡ ገደሉ ፡ ለበደልን ፡ ላጎደልነው ፡ ሁሉ
ንስሀ ፡ እንገባለን ፡ ፊትህ ፡ ጌታ ፡ ሆይ ፡ ይምጣልን ፡ ምህረትህ
______________________________________________________________
በሳር ፡ ብንሰራ ፡ ባገዳ
ተቃጥሎብን ፡ እንዳንጎዳ
የሚያነጥር ፡ እሳት ፡ ሲመጣ
ማነው ፡ ተፈትኖ ፡ ሚወጣ
አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ ምለምንህ ፡ (እለምንሀለው) ፡ አንድ ፡ ነገር
የኖርኩትን ፡ ኑሮ ፡ እንድናገር
የተናገርኩትን ፡ እንድኖር (፪x)
እርዳኝ ፡ በዚህ ፡ ዘመን
በጨለማ ፡ የተሰወረ ፡
በማስመሰል ፡ ኑሮ ፡ የኖረ
ወደ ፡ ብርሀን ፡ ታወጣለህ
ለሁሉም ፡ እንደስራው ፡ ትከፍላለህ
አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ ምለምንህ ፡ (እለምንሀለው) ፡ አንድ ፡ ነገር
የኖርኩትን ፡ ኑሮ ፡ እንድናገር
የተናገርኩትን ፡ እንድኖር (፪x)
እርዳኝ ፡ በዚህ ፡ ዘመን
አንዳንዱ ፡ ለደሞዝ ፡ ይሰብካል
ሌላኛው ፡ ለጥቅም ፡ ያመልካል
ታዲያ ፡ ማነው ፡ አንተን ፡ ፈላጊ
የተናገረውን ፡ አድራጊ
አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ ምለምንህ ፡ (እለምንሀለው) ፡ አንድ ፡ ነገር
የኖርኩትን ፡ ኑሮ ፡ እንድናገር
የተናገርኩትን ፡ እንድኖር (፪x)
እርዳኝ ፡ በዚህ ፡ ዘመን
ባፌ ፡ ብዙ ፡ ፍቅርን ፡ ስገልጥ
ወንድሜን ፡ በነገር ፡ ስረግጥ
ቃል ፡ አባይ ፡ ሆኜ ፡ እንዳልገኝ
ጌታ ፡ ሆይ ፡ ከሀሰት ፡ ጠብቀኝ
አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ እኔ ፡ ምለምንህ ፡ (እለምንሀለው) ፡ አንድ ፡ ነገር
የኖርኩትን ፡ ኑሮ ፡ እንድናገር
የተናገርኩትን ፡ እንድኖር (፪x)
እርዳኝ ፡ በዚህ ፡ ዘመን
በጓዳም ፡ ይሁን ፡ በጎዳና
ነውር ፡ የሌለባት ፡ ህሊና
በእግዚአብሄርና ፡ በሰው ፡ ፊት
እንድራመድ ፡ እርዳኝ ፡ በእውነት
____________________________________________________
አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በየቀኑ ፡ መጨረሻ
ለትውልድ ፡ መፈወሻ ፡ አድርገኝ
አንተን ፡ በመፍራት ፡ አሳድገኝ
ቅጠሌን ፡ አይተው ፡ የተነሰጡ
ፍሬን ፡ ፍለጋ ፡ ቤቴ ፡ ስነጡ
በጣፋጭ ፡ ዜማ ፡ እየጠራሁኣቸው
ያለ ፡ ዉሃ ፡ እንዳሸኛቸው ፡ ።
አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በየቀኑ ፡ መጨረሻ
ለትውልድ ፡ መፈወሻ ፡ አድርገኝ
አንተን ፡ በመፍራት ፡ አሳድገኝ
ስምህ ፡ ተጠርተው ፡ ድንቅን ፡ ስሰራ
የኔ ፡ ገድል ፡ እንዳይወራ
መድረኩም ፡ እንኳ ፡ ብነቃነቅ
አንተን ፡ አክብሬ ፡ ራሴን ፡ ልናቅ።
አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በየቀኑ ፡ መጨረሻ
ለትውልድ ፡ መፈወሻ ፡ አድርገኝ
አንተን ፡ በመፍራት ፡ አሳድገኝ
የውርንጫዋ ፡ የስራ ፡ ድርሻ
ወደ ፡ ኢየሩሳሌም ፡ መድረሻ
ጨርቅ ፡ ብነጠፍ ፡ ሆሳዕና ፡ ብባል
ክብር ፡ ስግደትም ፡ ላንተ ፡ ይገባል።
አዝ፦ ጌታ ፡ ሆይ ፡ በየቀኑ ፡ መጨረሻ
ለትውልድ ፡ መፈወሻ ፡ አድርገኝ
አንተን ፡ በመፍራት ፡ አሳድገኝ
ባመጽ ፡ ተወልደን ፡ በኃጢኣት ፡ አድጋናል
በጎውን ፡ ነገር ፡ ማን ፡ ያሳየናል
በሚለው ፡ ትውልድ ፡ መካከል ፡ ስገኝ
እውነትን ፡ ገላጭ ፡ ብርሃን ፡ አድርገኝ።
________________________________________
አዝ፦ ዲያቢሎስ ፡ ምነው ፡ ቸኮለ ፡ ሊውጠን ፡ እየከጀለ
መሰለኝ ፡ ቀኑ ፡ ሊደርስ ፡ የሰይጣን ፡ መንግስት ፡ ሊፈርስ
በእርግጥ ፡ ቀኑ ፡ ደርሶ ፡ ነው ፡ የሚይዘው ፡ ግራ ፡ ገብቶት ፡ ነው (፫x)
የገባው ፡ ደረቱን ፡ ነፍቶ ፡ ነጋሪት ፡ ከበሮ ፡ መቶ
ሲወጣ ፡ በጣር ፡ ተይዞ ፡ በጌታ ፡ ኢየሱስ ፡ ስም ፡ ታዞ ፡
አይተናል ፡ ዛሬም ፡ ይሆናል ፡ የኢየሱስ ፡ ስሙ ፡ ያድናል
አዝ፦ ዲያቢሎስ ፡ ምነው ፡ ቸኮለ ፡ ሊውጠን ፡ እየከጀለ
መሰለኝ ፡ ቀኑ ፡ ሊደርስ ፡ የሰይጣን ፡ መንግስት ፡ ሊፈርስ
በእርግጥ ፡ ቀኑ ፡ ደርሶ ፡ ነው ፡ የሚይዘው ፡ ግራ ፡ ገብቶት ፡ ነው (፫x)
ሌባ ፡ ነው ፡ ነፍስን ፡ ይሰርቃል ፡ ከህይወት ፡ መንገድ ፡ ያርቃል
አይገባም ፡ በዋናው ፡ በር ፡ ይያዛል ፡ መስኮት ፡ ሲሰብር
ሲሸፍት ፡ እንደ ፡ ልማዱ ፡ ደቆሰው ፡ ኢየሱስ ፡ በክንዱ
አዝ፦ ዲያቢሎስ ፡ ምነው ፡ ቸኮለ ፡ ሊውጠን ፡ እየከጀለ
መሰለኝ ፡ ቀኑ ፡ ሊደርስ ፡ የሰይጣን ፡ መንግስት ፡ ሊፈርስ
በእርግጥ ፡ ቀኑ ፡ ደርሶ ፡ ነው ፡ የሚይዘው ፡ ግራ ፡ ገብቶት ፡ ነው (፫x)
አድራሻው ፡ አመድ ፡ አተላ ፡ እንደ ፡ ከብት ፡ አሳር ፡ ሲያበላ
የለውም ፡ ክብር ፡ ማእረግ ፡ አያውቅም ፡ ሰው ፡ ማሳደግ
ኢየሱስ ፡ አዳነን ፡ ከእጁ ፡ ሆ ፡ በሉ ፡ ስሙን ፡ አውጁ
አዝ፦ ዲያቢሎስ ፡ ምነው ፡ ቸኮለ ፡ ሊውጠን ፡ እየከጀለ
መሰለኝ ፡ ቀኑ ፡ ሊደርስ ፡ የሰይጣን ፡ መንግስት ፡ ሊፈርስ
በእርግጥ ፡ ቀኑ ፡ ደርሶ ፡ ነው ፡ የሚይዘው ፡ ግራ ፡ ገብቶት ፡ ነው (፫x)
ለመስቀል ፡ እንጨት ፡ ሲቆርጥ ፡ መዶሻ ፡ ሚስማር ፡ ሲሰጥ
መቃብር ፡ ድንጋይ ፡ ሲገጥም ፡ ዘብ ፡ ሲያቆም ፡ ማእተም ፡ ሲያትም
ፈርቶ ፡ ነው ፡ ይህ ፡ ሁሉ ፡ አበሳ ፡ አልቀረም ፡ ኢየሱስ ፡ ተነሳ