ረብጣ ዶላር ያስገኘው የኤሌከትሪክ ሽያጭ! የሃይል አቅርቦቱን 100% የማድረስ እቅዱ! | The Plan to Achieve 100% Energy Access!
Gebeya Media - ገበያ
0:00 / 0:00
ረብጣ ዶላር ያስገኘው የኤሌከትሪክ ሽያጭ! የሃይል አቅርቦቱን 100% የማድረስ እቅዱ! | The Plan to Achieve 100% Energy Access!
3 629 просмотров · 1 день назад
Gebeya Media - ገበያ
664 тыс. подписчиков
3 629 просмотров · 1 день назад
የኢትዮጵያ የንጹህ ታዳሽ ኃይል ልማት ፍሰት ከሀገር ውስጥ ፍጆታ ባለፈ ለቀጣናው ኢኮኖሚያዊ ትስስር እና የውጭ ምንዛሪ ግኝት ቁልፍ ሚና እየተጫወተ መምጣቱ በተግባር እየታየ ነው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸም እንደሚያሳየው፣ ተቋሙ በዓመቱ ያስመዘገበው ድምር ውጤት ሀገሪቱ በሃይድሮ ፓወር እና በሌሎች ታዳሽ ኃይል መስኮች ላይ የያዘችው ስትራቴጂካዊ ርዕይ ወደ ተጨባጭና የላቀ ውጤት እየተሸጋገረ መሆኑን የሚያረጋግጥ ነው። በበጀት ዓመቱ ከውጭ ሀገራት የኃይል ሽያጭ ብቻ 475 ነጥብ 7 ሚሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ አሸብር ባልቻ በይፋ ተናግረዋል። ይህ አኃዝ ከቀድሞው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ25 በመቶ ዕድገት ያሳየ ሲሆን ኢትዮጵያ ለጎረቤት ሀገራት የምታደርገው የኃይል አቅርቦት እያደገ መሄዱን እና የቀጣናው የኢነርጂ ማዕከል የመሆን አቅሟን በግልጽ ያሳያል። በአጠቃላይ ከተመረተው የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ የውኃ ማመንጫዎች 97 በመቶ ድርሻ መያዛቸው ደግሞ ሀገሪቱ ያላትን ሰፊ የተፈጥሮ ጸጋ ለአካባቢ ጥበቃ ተስማሚ በሆነ መንገድ እየተጠቀመችበት መሆኑን ያመላክታል። የማመንጨት አቅሙን 9 ሺህ 730 ሜጋ ዋት ማድረስ የቻለውና የ23 በመቶ ዕድገት ያስመዘገበው የዘንድሮው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አፈጻጸም፣ በተቋሙ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ የ124 ነጥብ 2 ቢሊዮን ብር ጠቅላላ ገቢ በመሰብሰብ የ39 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር የተጣራ ትርፍ እንዲመዘገብ አስችሏል። የዕቅዱን 101 ነጥብ 83 በመቶ ማሳካት መቻሉ የስትራቴጂክ እቅድ አፈጻጸም ብቃትን ብቻ ሳይሆን፣ የኢትዮጵያን የረጅም ጊዜ የኢኮኖሚ ነፃነት እና የዲፕሎማሲ ተጽዕኖ ፈጣሪነት ከፍ የሚያደርግ ነው።
በእለቱ የገበያ ቢዝነስ ልዩ ትንቅር ዝግጅታችን የኢትዮጳያ ኤሌክትሪክ ሃይል አስመዘገብኩት ያለውን የ475. 7 ሚሊዮን ዶላር የኤሌክትሪክ ሃይል ሽያጭ መነሻ በማድረግ ለመሆኑ ይህ ካለፉት አመታት ጋር በንፅፅር ሲታይ ከፍተኛ የሆነ ገቢ እንዴት ሊመዘገብ ቻለ? ይህ ገቢ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ፍላጎት ላላት ኢትዮጵያ ምን ማለት ነው? ኢትዮጵያ በታዳሽ ሃይል ዘርፉ ያላት አቅምስ እንዴት ይታያል? የሚታዩ እንቅስቀሴዎች ኢትዮጵያ በአውሮፓውያኑ 20230 የመቶ ፐርሰንት የኤሌክተሪክ ሃይል ለማዳረስ ካስቀመጠችው ግብ አንፃር ምን አንድምታ አለው የሚሉትንና ተያያዥ ጉዳዮችን እንመለከታለን፡፡
ቻናላችንን ሰብስክራይብ፣ ይህንን ቪድዮ ላይክ እና ኮሜንት በማድረግ አብራችሁን ትቆዩ ዘንድ በአክብሮት እንጋብዛለን፡፡
The flow of Ethiopia's clean renewable energy development is visibly playing a key role not only for domestic consumption, but also for regional economic integration and foreign exchange earnings. The 2018 fiscal year performance of Ethiopian Electric Power (EEP) demonstrates that the institution's accumulated results for the year confirm that the country's strategic vision in hydropower and other renewable energy sectors is transitioning into concrete and superior outcomes. During the fiscal year, EEP Chief Executive Officer Ashebir Balcha officially stated that a revenue of 475.7 million dollars was generated from electricity sales to foreign countries alone. This figure shows a 25 percent growth compared to the same period of the previous year, clearly indicating Ethiopia's growing electricity supply to neighboring countries and its potential to become the energy hub of the region. Furthermore, the fact that water power plants account for 97 percent of the total generated electricity indicates that the country is utilizing its vast natural resources in an environmentally friendly manner. The current performance of Ethiopian Electric Power, which managed to reach a generation capacity of 9,730 megawatts and registered a 23 percent growth, enabled the generation of 124.2 billion birr in total revenue and a net profit of 39.5 billion birr for the first time in the institution's history. Achieving 101.83 percent of the plan demonstrates not only strategic planning execution efficiency, but also elevates Ethiopia's long-term economic independence and diplomatic influence.
In today's special business analysis program, using EEP's reported 475.7 million dollar electricity sales as a starting point, we will examine: How was such high revenue generated compared to previous years? What does this revenue mean for Ethiopia, a country with a high demand for foreign currency? How is Ethiopia's potential in the renewable energy sector viewed? And what implications do these visible developments have in relation to Ethiopia's goal of achieving 100 percent electricity access by the year 2030, alongside other related issues? We respectfully invite you to stay with us by subscribing to our channel, liking, and commenting on this video.
#GebeyaMedia #GebeyaBusiness #GebeyaSpecialProgaram #GbebeyaNews #businessNews #Ethiopia #RenewableEnergy #EthiopianElectricPower #GreenEnergy #HydroPower #EastAfrica #EnergyHub #EconomicGrowth #ForeignExchange #CleanEnergy #SustainableDevelopment #EnergyAccess2030