Перейти к содержимому

የ100 ቢሊዮን ብሩ የማጠናከሪያ ኩባንያ! ለደሃውና ለደመወዝተኛው ምንድነው? | 100 Billion Birr Mortgage Company!

Gebeya Media - ገበያ

0:00 / 0:00

የ100 ቢሊዮን ብሩ የማጠናከሪያ ኩባንያ! ለደሃውና ለደመወዝተኛው ምንድነው? | 100 Billion Birr Mortgage Company!

4 215 просмотров · 4 дня назад
Gebeya Media - ገበያ
664 тыс. подписчиков
4 215 просмотров · 4 дня назад
የኢትዮጵያ መንግሥት በሀገሪቱ የቤት ልማትና የፋይናንስ ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት እና የዜጎችን የረጅም ጊዜ የቤት ባለቤትነት ጥያቄ መሠረታዊ በሆነ መንገድ የሚመልስ ታላቅ ውጥን ይፋ አድርጓል። ጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ ይፋ እንዳደረጉት የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ እና የዓለም አቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን በጋራ በመሆን በግንባታውና በፋይናንስ ዘርፉ ውስጥ ከፍተኛ ሚና የሚጫወት እና በመጀመሪያው ምዕራፍ አንድ መቶ ቢሊዮን ብር ካፒታል የሚቋቋም የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ ለማቋቋም በትላንትናው እለት ስምምነት ላይ ደርሰዋል። ይህ ተቋም የሀገሪቱን የባንክ ዘርፍ ፈተናዎች ከመቅረፍ ባለፈ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ዜጎችን የኑሮ ደረጃ ከፍ የሚያደርግ እና የከተሞችን መልክ የሚቀይር ግዙፍ አሰራር እንደሆነም እየተገለጸ ነው። በኢትዮጵያ ያለው የቤት ባለቤትነት ፍላጎት ከዕለት ወደ ዕለት እያደገ ባለበት በዚህ ወቅት የዚህ ተቋም መቋቋም የረጅም ጊዜ የገንዘብ እጥረት ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ሰፊ ዕድሎችን የሚከፍት መሆኑም እየተነገረ ነው። በእለቱ የገበያ ቢዝነስ ልዩ ዝግጅታችንም ለመሆኑ ይህ በኢትዮጰያ እና በአለማቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽን ትብብር እንደሚቀዋቋም በትላንትናው እለት ይፋ የተደረገው የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያ እንዴት ይሰራል? በኢትዮጵያ ዕየታየ ያለውን ከፍተኛ የመኖሪያ ቤት ባለቤትነት ጥያቄኝ እንዴት ይፈታል? በአጋርነት የሚሰራው አለማቀፉ የፋይናንስ ኮርፖሬሽንስ ማን ነው? የቤት መግዣ ብድር መልሶ ማጠናከሪያ ኩባንያው ምን አይነት ሚናዎችን ይኖሩታል? ከባንኮች ጋር እና ከቤት አልሚዎች ጋርስ እንዴት ሊሰራ ይችላል? የሚሉትንና ተያያዥ ጉዳዮችን እንመለከታለን፡፡ ቻናላችንን ሰብስክራይብ ፣ ይህንን ቪድዮ ላይክና አስተያያት ካላችሁ ደግሞ ኮሜንት እያደረጋችሁ አብራችሁን ትቆዩ ዘንድ እንጋብዛለን፡፡ The Ethiopian government has unveiled a grand initiative that opens a new chapter in the country's housing development and financial history, fundamentally addressing citizens' long-term homeownership demands. As announced by Prime Minister Abiy Ahmed, the National Bank of Ethiopia and the International Finance Corporation (IFC) reached an agreement yesterday to establish a Mortgage Refinancing Company with an initial capital of 100 billion Birr, playing a major role in the construction and financial sectors. It is being stated that this institution is a massive operation that will not only resolve the banking sector's challenges in the country but also elevate the living standards of millions of citizens and transform the landscape of cities. At a time when the demand for homeownership in Ethiopia is growing day by day, it is also being said that the establishment of this institution will sustainably solve long-term capital shortage problems and open up vast opportunities. In today's special Business Market program, we examine how this Mortgage Refinancing Company—announced yesterday through the cooperation of Ethiopia and the International Finance Corporation—works; how it will solve the high demand for residential homeownership being seen in Ethiopia; who the International Finance Corporation partnering in this endeavor is; what roles the Mortgage Refinancing Company will have; and how it can work with banks and real estate developers, among related issues. We invite you to stay with us by subscribing to our channel, liking this video, and commenting if you have any feedback. #GebeyaMedia #GebeyaBusiness #GebeyaSpecialProgram #GebeyaNews #GebeyaPodcast #Ethiopia #HousingDevelopment #MortgageRefinancing #IFC #NationalBankOfEthiopia #RealEstate #EthiopianEconomy #BusinessNews